በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርሰትያን በኦታዋ የ ሀ የዝማሬ አገልግሎት ወነኛ አላማ ጌታ እግዚአብሔር አምላክን በዝማሬ በመንፈሳዊ ቅኔ እና በምስጋና በእውነትና በመንፈስ እግዚአብሔርን ማምለክሲ ሆን፡ በቀጣይነት የእግዚአብሔር ቤተሰቦች ካሉበት ከህይወት ጥያቄ ባሻገር የአምላኩን ታላቅነት አሳይቶ ለአምልኮና ለምስጋና እንዲነሳ ማድረግ፡፡
የእግዚአብሔር ህዝብ ካልሆነለት ወይም ካልተከናወነለት ጉዳዮች ይልቅ አሁን በእጁ ባለው ነገር ጌታውን ማመስገን እንዲጀምር መንፈሱን ማንቃት ፣ እንዲሁም ትላንት በህይወቱ እግዚአብሔር ያደረገለትን በማስታወስ፣ባልተፈፀመለት ጉዳዩ ላይ ሆኖ ወይንም በደረሰበት ምድራዊ መከራና ችግር ላይ ሆኖ ጌታውን በዚህ ሁሉ እንዲያመሰግን ማድረግ ነው፡፡ በሌላ አባባል በሐዋሪያት ስራ 16፣ 25 ላይ እንደተፃፈው የጳውሎስንና የሲላስን የህይወት ተሞክሮ በዚህ ዘመን ቅዱሳን ህይወታቸው እንዲያደርጉት እና እንዲለማመዱት በማስተማር ፡በመምከር በተግሳፅ የእግዚአብሔርን ህዝብ ለማቅናት ይተጋል፡፡